የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል ዓባላት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ  አካሄዱ

የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል ዓባላት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ አካሄዱ

Feb 17, 2026

ዩኒቨርሲቲው በአካዳሚክ ዘርፍ፣ በአስተዳደር ዘርፍ እና ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ዘርፍ እንዲሁም በጎባ ጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ እና በሻሸመኔ ካምፓስ ላለፉት 6 ወራት ሲሰሩ የቆዩ ስራዎች ቀርበው በካውንስል ዓባላት ተገምግመዋል።


የካውንሉ ዓባላት በቀረበው ሪፖርት ላይ በርካታ ጥያቄ እና ሃሳብ ያነሱ ሲሆን፣ በዘርፉ አመራሮች ሃሳብ እና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።

የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና የሥራ አፈፃፀም ግምገማውን የመሩ ሲሆን በግምገማው ሥነ-ሥርዓት ላይ መዝጊያ ባደረጉት ማጠቃለያ ተቋሙ በለውጥ ውስጥ መሆኑን አመላክተው በዩኒቨርሲቲው በየሥራ ክፍሎች ባለፉት 6 ወራት ካከናወንናቸው ተግባራት ከተረካከብናቸው ቁልፍ ውጤት አመልካቾች ( KPI) አንፃር የተከናወኑና ያልተከናወኑት ተግባራት ተለይተው የተገመገሙበት፣ ስራዎቹ በመሰራታቸው የመጣው ለውጥና ተፅኖ እንዲሁም የትኛው ዘርፍ እና የሥራ ክፍል በታለመውና በታቀደው አግባብ ተልዕኮውን እየተወጣ እንደለ በመለየት ፣ በሂደቱም ጠንካራና ቁርጠኛውን አመራር ከለዘብተኛው ለመለየትና ለተሻለ ተቋማዊ ለውጥ ለማቀድ እድል ፈጥሮልናል ብለዋል።


Event Gallery

Gallery image 1
Gallery image 2
Gallery image 3
Gallery image 4
Gallery image 5
Gallery image 6
Gallery image 7
Gallery image 8
Gallery image 9

Related Articles

View All